ከ ፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ዝግጅት ጋር በተያያዘ በሀገራቸው ምንም የሽብር ስጋት እንደሌለ የፈረንሳይየስፖርት ሚንስትር የሆኑት አሜሊ ኦውዴያ፡ካስቴራ ሰሞኑን ፍራንስ 2 በሚባለዉ የቴሌቪዥን ጣቢያ በቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ አረጋግጠዋል ።
አሜሊ ኦውዴያ ካስቴራ ስለ ኦሎምፒክ ጨዋታዎች የደህንነት ስጋት እንደሌለ ቢገልፁም ነገሮችን ለማረጋጋት እስከ ሰኔ 12 ድረስ የመክፈቻዉን እለት ትርኢት የሚያቀርቡት በሙሉ እይታ ልምምዱን በቦታዉ ላይ እንደማያደርጉ እና ለሌላ ጊዜ መተላለፉን ተከትሎ በሴይን ላይ የሚካሄደው የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት አዘጋጆቹ እየሠሩበት ያለው “ማዕከላዊ ዕቅድ” ሆኖ እንደቀጠለም አክለዉ ገልፀዋል ።
ከአሸባሪዎች ስጋት አስፈላጊውን ሁሉ የሚመለከታቸው አካላት በጥንቃቄ እየተከታተሉ መሆኑንም ሚኒስትሯ አስረድተዉ ።

ይህ የተፈራዉ ሽብር ቢያጋጥም ሌላ ሁለተኛ አማራጭ እንዳለ ለተጠየቁት መልስ የሰጡት አሜሊ ኦውዴያ “እስከሚያዉቁት ሀገራቸዉን በዚህ በኦሎምፒክ ዝግጅት ከሌላዉ ጊዜ በተለየ የሽብር ስጋት የለም” ሲሉ አረጋግጠዋል።
በርግጥ የፈረንሣይ መንግሥት ከመጋቢት 22 በሞስኮ አቅራቢያ በሚገኘው የኮንሰርት አዳራሽ ላይ ከተፈጸመው የሽብር ጥቃት በኋላ ሀገራቸዉ ፈረንሳይ የደኅንነት ዕቅዷን ወደ ከፍተኛው ደረጃ ከፍ ለማድረግ መወሰኗን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በእ.ኤ.አ ሐምሌ 26 2024 ለሚካሄደው የመክፈቻ ስነ ስርዓት እቅድ ሁለት እንደሌለ በድጋሚ ለተጠየቁት ሚኒስትሯ ሲመልሱ “ይህ በሴን ወንዝ ላይ የሚደረገው የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት የእኛ ማዕከላዊ እቅዳችን ነው ። መከበር ያለበትም የታቀደዉ ቦታ ላይ ነዉ።
የቴክኒክ ሙከራዎች እና ሌሎችም ልምምዶች ከታቀደዉ ቀን ለዉጥ እንደተደረገባቸዉም ከሳምንታት በፊት አሳዉቀናል” ሲሉ ለጥያቄዎቹ መደምደሚያ ሰጥተዋል።
ቲም ኢትዮጵያ 2024 ፓሪስ
#ሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን 💫

admin
Author: admin